Saturday, December 7, 2013

ኔልሰን ማንዴላ በሕይወት ቢለዩንም በመንፈስ አብረውን ይቆያሉ




http://www.ginbot7.org/

በአፓርታይድ የደቡብ አፍሪቃ መንግሥት ብቻ ሳይሆን በዩ. ኤስ. አሜሪካ ጭምር ሽብርተኛ ተብለው ሲሳደዱ፣ ሲታሰሩና ሲሰቃዩ የሕይወታቸውን አጋማሽ የጨረሱ፤ በመሣሪያ የታገዘ አመጽንና ሕዝባዊ እምቢተኝነትን አጣምሮ የያዘ ሁለ-ገብ ትግል በመምራት ለአፓርታይድ አገዛዝ ማብቃት ከፍተኛ ድርሻ ያለው የትግል አስተዋጽዖ ያደረጉ፤ ለመላው ዓለም የነፃነት ታጋዮች አርአያ የሆኑት ኔልሰን ማንዴላ አረፉ።
ኔልሰን ማንዴላ የነፃነት ትግልን በግንባር በመሰለፍ መርተዋል። ኢትዮጵያ ድረስ በመምጣት ወታደራዊ ሥልጠና ወስደው ዘረኛዉን የፕሪቶሪያ አገዛዝ በመሣሪያ ታግለዋል። የእሳቸው ጠመንጃ ማንሳት ለበርካታ ወጣት ታጋዮች አርዓያ ሆኗል። እስር ቤት በቆዩባቸው 27 ዓመታት ደግሞ የድርጅታቸውንና የትግሉን አመራሩ ለጓዶቻቸው በመተው እርሳቸው ለነፃነትና ለእኩልነት በመታሰርና ስቃይን በመቀበል ትግሉን መርተዋል። በዚህም ምክንያት በትግል ሜዳም በእስር ቤትም መሪ እንደሆኑ የዘለቁ ታላቅ አፍሪቃዊ ናቸው።
ከነፃነት በኋላ ደግሞ ኔልሰን ማንዴላ በሕዝብ ነፃ ፈቃድ የተመረጡ የአዲሲቷ ደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያ ፕሬዚዳንትነት ሆነዋል። በየምርጫው ተወዳድሬ አሸንፌ በፕሬዚዳንትነት ልቀጥል ሳይሉ በአፍሪቃ ባልተለመደ ሁኔታም አንድ ዙር ብቻ አገልግለው ደግመው ላለመወዳደር ወስነው በጊዜ ሥልጣናቸውን በመልቀቅ መርተዋል። በመሆኑም ኔልሰን ማንዴላ ሥልጣን ላይ ሆነውም ሥልጣን ለቅቀውም መሪ መሆን የቻሉ ድንቅ አፍሪቃዊ ናቸው።
ኔልሰን ማንዴላ ታላቅ የነፃነት አርበኛ፣ ታላቅ የለውጥ አራማጅ፣ ታላቅ መምህር እና ታላቅ የእርቅ ሰው ነበሩ። ዛሬ ዓለም እኚህን ታላቅ አፍሪቃዊ አጣች።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በኔልሰን ማንዴላ ሕልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ይገልፃል። ከእንግዲህ ማንዴላን የምናስባቸው ከእሳቸው ተሞክሮ የምንማረው ሲኖር ነው። በዘረኝነት እየተጠቃን ላለነው ኢትዮጵያዊያን የማንዴላ ትምህርት ሕያው ሊሆን ይገባል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ ዘረኝነትን በጽናት የመታገል ሆኖም ግን ይቅር ባይ የመሆንን እሴቶች ተግባራዊ በማድረግ ማንዴላ በሕይወት ቢለዩንም በመንፈስ ሁሌም አብረውን እንዲኖሩ እናድርግ ይላል።
የግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ህዝብ ግንኙነት
   Posted By Samuale Tewlde

ማንዴላ


ከዳንኤል ክብረት

አንዳንዱ የሞተበት ቀን የድል ቀን ተብሎ ይከበርበታል፤ ሕዝብ የመሞቻውን ቀን የሚናፍቁለት ሰውም አለ፡፡ አንዳንዱ እንኳን ተወለደ ሳይባልለት እንኳን ሞተ ይባልለታል፡፡ አንዳንዱ እንዲሞት ይጸለይለታል፤ ሌላው እድሜው እንዲያጥር ይረገማል፡፡ ከዚህ የተለየ ነው ማንዴላ፡፡
ሚሊየኖች እንዳይሞት የሚጸልዩለት፤ ሚሊየኖች እንዲኖር የሚመኙለት፤ ሚሊየኖች ከእድሜያቸው ተቀንሶ ቢሰጠው የሚፈቅዱለት፤ ሚሊየኖች እነርሱ ሞተው ሊያኖሩት የሚሹት፤ ሚሊየኖች በየቀኑ የጤናውን ሁኔታ ከራሳቸው ጤና በላይ የሚከታተሉለት ሰው ነው ማንዴላ፡፡

አፍሪካ አያሌ መሪዎችን በቅርብ ዘመናችን አስተናግዳለች፡፡ አያሌ የነጻነት ታጋዮችን አይታለች፡፡ እንደማንዴላ ታሥረው የታገሉ ነበሩ፡፡ እንደ ማንዴላ ድርጅት አቋቁመው የተዋጉ ነበሩ፤ እንደ ማንዴላ ሕዝባቸውን ለነጻነት ያበቁ ነበሩ፤ እንደ ማንዴላም ከነጻነት በኋላ የመጀመሪያው የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት የሆኑም ነበሩ፤ እንደ ማንዴላ ከሀገር ተሰደው የኖሩ ነበሩ፤ ታድያ ማንዴላን ምን ልዩ አደረገው?
ማንዴላ የታገለው ለፍትሐዊነት ነው፡፡ ደጋግሞ ይናገር እንደ ነበረው ‹‹እኛ የታገልነው የነጭ የበላይነትን በጥቁር የበላይነት ለመተካት አይደለም፤ የታገልነው ነጮች፣ ጥቁሮችና ሌሎች በእኩልነት የሚኖሩባትን ደቡብ አፍሪካ ለመመሥረት ነው›› ይል ነበር፡፡ በብዙ የአፍሪካ ሀገሮች ከነጻነት ትግል በኋላ ጭቆና አልቀረም፡፡ ነገር ግን ነጭ ጨቋኞች በጥቁር ጨቋኞች ተተክተዋል፡፡ በነጮች ተይዞ የነበረው የገዥነት ቦታ ለሥልጣን በበቁት ታጋዮች ፓርቲዎችና ጎሳዎች ተተካ፡፡ የነጻነት ተዋጊዎች የፍትሕና እኩልነት አስፋኞች ሳይሆኑ አዳዲሶቹ ገዥ መደቦች ሆነው ብቅ አሉ፡፡ በነጮች ተይዞ የነበረውን ሀብት ነጻ አውጭ ግንባሮችና ፓርቲዎች ወረሱት፡፡ ስለዚህም ሕዝቡ በትግሉ ጨቋኞችን በሌሎች ጨቋኞች ተካቸው እንጂ ፍትሕና እኩልነትን ለማግኘት አልታደለም፡፡
ማንዴላ ይህንን ነበር የተዋጋው፡፡ እንደተመረጠ ብዙዎች የነጮች መሬት ተቀምቶ ለጥቁሮች እንዲሰጥ፣ ነጮች ከሀገሪቱ እንዲባረሩ ይፈልጉ ነበር፡፡ እርሱ ግን አላደረገም፡፡ ‹መሬቱ ፍትሐዊ በሆነ መልኩ እንዲዳረስ እንጂ መሬት አልባ ነጮች የመፍጠር ዕቅድ የለንም› አለ፡፡ ጥቁሮች ይበልጥ ነጻ የሚወጡት የበለጸገች ደቡብ አፍሪካ ስትኖር እንጂ በደኸየች ደቡብ አፍሪካ ውስጥ አይደለም ብሎ አመነ፡፡ ለዚህ ደግሞ የብዙ ዘመን ሀብትና ልምድ ያላቸው ነጮች ወሳኞች መሆናቸውን ተገነዘበ፡፡ ለዚህም ነበር በሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ያየነው ምስቅልቅል በደቡብ አፍሪካ ያልተከሰተው፡፡
ማንዴላ የዕርቅና የፍቅር ሰው ነበር፡፡ በነጮችና በጥቁሮች መካከል ለዘመናት በአፓርታይድ የተፈጠረውን መከፋፈል፣ መጠላላትና መገፋፋት በዕርቅና በይቅር ባይነት እንጂ በመሣሪያና በበቀል ሊጠፋ እንደማይችል የተረዳ መሪ ነው፡፡ አፓርታይድ ሲገረሰስ የይቅርታ ኮሚሽን ተቋቁሞ፣ ነባር የሕዝብ ለሕዝብ ችግሮች በተቻለ መጠን በይቅርታና በዕርቅ እንዲወገዱ ሠርቷል፡፡ በአንዳንድ የአፍሪካ ሀገሮች ከነጻነት በፊት የነበሩ ገዥዎችና አበሮቻቸው ወደ እሥር ቤት ሲወረወሩና ወደ ውጭ ሲሰደዱ፤ በደቡብ አፍሪካ ግን የከፋ ወንጀል ካልፈጸሙና ይቅርታ ለመጠየቅም ከፈቀዱ ችግሩን በዕርቅና በይቅርታ ለመፍታት ተችሏል፡፡ በዚህም ደቡብ አፍሪካን ከአፓርታይድ ብቻ ሳይሆን ሀገርን አፍርሶ ከመሥራት አባዜ ነጻ እንድትወጣ አድርጓታል፡፡
ማንዴላ ለሰዎች ልጆች ሁሉ የቆመ መሪ ነበረ፡፡ ከዊኒ ማንዴላ ጋር ያፋታቸው ዋነኛው ምክንያት ዊኒ ማንዴላ በነጻነት ትግሉ ወቅት ‹ለነጻነት ትግሉ› ሲባል ፈጽመውታል የተባለው ኢ ሰብኣዊ ድርጊት በእርቅና ይቅርታ ኮሚሽኑ መጋለጡ ነበር፡፡ ምንም እንኳን ለነጻነት ትግሉ ሲባል ቢደረግም፣ ምን እንኳን ዊኒ ማንዴላ ቢሆኑም ማንዴላ ግን ሊታገሡት አልቻሉም፡፡ የነጻነት ታጋይ ድርጅቱ ኤ ኤን ሲ በትጥቅ ትግሉ ጊዜ የፈጸማቸው ኢሰብአዊ ድርጊቶች ካሉ ይቅርታ የመጠየቅ ግዴታ አለበት ብለው የሚያምኑት ማንዴላ በዚህ ምክንያት ከዊኒ ጋር ተለያይተዋል፡፡ ከነጻነት በኋላ አያሌ የነጻነት ታጋይ ድርጅቶች በትጥቅ ትግላቸው ወቅት የፈጸሙት ኢሰብአዊ ድርጊት፣ ወንጀልና ግፍ ተሠውሮ እንዲቀር ሲደረግ ማንዴላ ግን ኤ ኤን ሲ ይቅርታ እንዲጠይቅ አድርገዋል፡፡
ማንዴላ ሰላማዊ መንገድን ብቻ ይመርጥ የነበረ መሪ ነበር፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ምንም እንኳን የትጥቅ ትግል ሲያካሂድ የነበረውን ኤ ኤን ሲ የመራ ቢሆንም ሰላማዊ የትግል መንገድ ከማንኛውም የትግል መንገድ ሁሉ ቅድሚያ እንዲያገኝ ሲታገል የኖረ ሰው ነው፡፡ ይህ ትግሉ ከአፓርታይድ መሪዎች ጋር ብቻ ሳይሆን በኤ ኤን ሲ ውስጥ ከነበሩ ሌሎች አመራሮች ጋርም ጭምር ነበር፡፡ የጠመንጃ ትግል ለሰላማዊ ትግል፣ ለድርድርና ለውይይት የተዘጋውን በር ማስከፈቻ እንጂ ሰላማዊ መንግሥት የመመሥረቻ መንገድ አይደለም ብሎ ያምን ነበር፡፡ በአፓርታይድ የመጨረሻዎቹ ዘመናት እነ ፒተር ቦታ ከኤ ኤን ሲ መሪዎች ጋር ለመደራደር ያቀረቡትን ጥያቄ አንዳንድ የድርጅቱ አመራሮች አልቀበል ሲሉ ‹እኔ ብቻዬንም ቢሆን እደራደራለሁ› እስከ ማለት አቋም ወስዶ  ነበር፡፡ ከአፓርታይድ ጋር የሚደረገው ትግል በጠመንጃ አሸናፊነት ሳይሆን በሃሳብ አሸናፊነት መጠናቀቅ አለበት የሚል አቋም ነበረው፡፡ 
በደቡብ አፍሪካ ሁሉንም ያሳተፈ የመጀመሪያ ምርጫ በተደረገ ጊዜ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ ሕገ መንግሥቱን ብቻውን ለማጽደቅ የሚያስችለውን ድምጽ አላገኘም ነበር፡፡ ይሄንን አጋጣሚ ማንዴላ በደስታ ነበር የገለጠው ‹‹ሁሉንም ሕዝብ የሚመራ ሕገ መንግሥት ብቻችንን ማጽደቅ የለብንም፤ ይህ አጋጣሚ መልካም ነው፤ ከሌሎቹ ጋር ተማክረን፣ ተደራድረንና ተስማምተን እንድናጸድቅ ያደርገናል› ብሎ ነበር፡፡
ማንዴላ ሥልጣን መያዝን ብቻ ሳይሆን መልቀቅንም ያስተማረ ሰው ነው፡፡ ማንዴላ ደቡብ አፍሪካን ለአንድ ዙር ብቻ ነው የመራው፡፡ በቀጣዩ ምርጫ ብቻ ሳይሆን ለብዙ ዘመናት በሚደረጉ ምርጫዎችም የማሸነፍ ዕድል ነበረው፡፡ ነገር ግን በቃኝ አለ፡፡ እየተወደደ፤ እየተመሰገነና እየተከበረ በቃኝ አለ፡፡ በደቡብ አፍሪካውያን ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ብሎም በመላው ዓለም ‹አይከን› የመሆንን ጸጋ ተጎናጸፈ፡፡ የነጻነት፣ የጽናትና የትዕግሥት፣ የሰላምና የዕርቅ፣ የይቅር ባይነትና ከጥላቻ ውጭ የሆነ ፖለቲካ ‹አየከን› ሆነ ማንዴላ፡፡ በመላው ዓለም ሕዝብ ልብ ውስጥ ማንም ሊነቅለው የማይችል ዛፍ፣ ማንም ሊያፈርሰው የማይችል ሐውልት ሆነ ማንዴላ፡፡
ለዚህ ይመስለኛል ማንዴላን ዓለም በሙሉ የሳሳለት፤ ለጤናውም ሆነ ለእድሜው የጸለየለት፤ የተጨነቀለትና ልቡን ከልቡ ጋር ያስተባበረለት፡፡ እንደ እርሱ ዓይነት ሰዎች እንደ ሄሊኮሜት በዘመናት አንድ ጊዜ ብቅ የሚሉ ናቸው፡፡ ተወደው ሥልጣን ላይ የሚቀመጡ፣ ተወደውም ከሥልጣን የሚወርዱ፤ ተወደውም ያለ ሥልጣን የሚኖሩ፡፡ እንደ ማንዴላ ዓይነት ሰው እንኳን ሌላው የአፍሪካ ሀገር ራሱ ኤ ኤን ሲም ዳግም ሊያገኝ አልቻለም፡፡ መከፋፈል ዕጣ ፈንታ የሆነውም በዚህ ምክንያት ነው፡፡
መሪነትና ባለ ሥልጣንነት ምን ያህል እንደሚለያዩ ማንዴላ አንድ ማሳያ ናቸው፡፡ ማንዴላ ባለ ሥልጣን አልነበሩም፤ መሪ እንጂ፡፡ ባለ ሥልጣን በሰው ገንዘብ ውስጥ እንጂ በሰው ልብ ውስጥ ቦታ የለውም፡፡ ባለ ሥልጣን ይፈራል እንጂ አይከበርም፤ ባለ ሥልጣን ቢሮ አለው እንጂ ሀገር የለውም፤ ባለ ሥልጣን የሚላላኩት ሠራተኞች እንጂ የሚጸልዩለት ወገኖች የሉትም፡፡ ባለ ሥልጣን የሚያዘው ሰው እንጂ የሚያፈቅረው ሰው አያገኝም፤ ባለ ሥልጣን ፊርማውን የሚፈልግ እንጂ እድሜውን የሚፈልግ የለም፤ ባለ ሥልጣን ብዙ ገንዘብ እንጂ ብዙ ልቦች አያገኝም፤ ባለ ሥልጣን ከሥልጣን ወዲህ እንጂ ከሞት ወዲያ ተዝካር የለውም፡፡ 
ማንዴላ ከሞት በኋላም ይኖራል፡፡ በብዙ ልቦች ውስጥ ይኖራል፡፡ መቃብር እርሱን ሊያስረሳ አይቻለውም፡፡ እርሱ ከመቃብር በላይ የሆነ ተግባር አለውና፡፡ ማንዴላ የአንድ ሀገር መሆኑ ቀርቶ የዓለም ሆኗል፡፡ መሬት ላይ የሚቆም ሐውልት አያስፈልገውም፤ እርሱ በሕዝቦች ልብ ውስጥ የማይፈርስ ሐውልት በሕይወት እያለ ሠርቷልና፡፡ ብዙ ባለ ሥልጣናት በሕይወት እያሉ በሰው ልብ ውስጥ ሐውልት መሥራት ስለማይችሉ፣ ከሞቱ በኋላ የድንጋይ ሐውልት ይሠራላቸዋል፡፡ ነገር ግን ሐውልታቸው መልእክት አልባ ሐውልት ይሆናል፡፡ እንደ ማንዴላ ያሉ መሪዎች በመሬት ላይ ሐውልት ሲተከልላቸው ደረቅ ሐውልት አይሆንም፤ መልእክት ያለው ሐውልት እንጂ፡፡
ማንዴላ አይሞትም፤ ጀግና አይሞትምና፤ የማንዴላ አይረሳም፤ ሕዝብ ልብ ውስጥ የገባ ሰው አይረሳምና፤ ማንዴላ አያልፍም፣ በጎ ሥራ አያልፍምና፡፡   
     posted Samuale Tewelde

Police In Thailand Lay Down Vests and Barricades In Solidarity With Protestors



http://politicalblindspot.com/police-in-thailand-lay-down-vests-and-barricades-in-solidarity-with-protestors/

In a stunning turn of events today in Thailand, riot police yielded to the peaceful protesters they were ordered to harass and block. They police removing barricades and their helmets as a sign of solidarity.
The protesters explain that their goal is to destroy the political machine of former Prime Minister Thaksin Shinawatra, who is accused of widespread corruption and abuse of power. Thaksin’s sister, Prime Minister Yingluck Shinawatra, is currently in power, and is seen as a puppet of her brother.

Suthep Thaugsuban, the leader of the widespread protests that have been going on in Thailand, told his supporters to storm the Bangkok Metropolitan Police Bureau. This was one of the primary buildings they vowed to take over in their plan to topple the Shinawatra government.
The move by police has surprised many, and marks a turning point in the protests and a potential shift in power.
Watch the video below, and let us know what you think: could something like this even happen in the West? In the United States?

 http://www.youtube.com/watch?v=t3y3WPL7Oko









Friday, December 6, 2013

Cry of migrant mothers, children in Saudi Arabia







ESAT News  November 27, 2013

Several Ethiopian mothers and children are suffering from hunger and thirst after the scheduled flight of several Ethiopian mothers and children who were to be repatriated to Ethiopia from Riyadh has been cancelled yesterday.

The mothers and children are crying for help. They say they have been thrown into the streets and are dying from lack of drinking water. ESAT has directly contacted the migrants.

Meanwhile, the International Organisation for Migration (IOM) has stated that it has assisted over 21,000 Ethiopian returnees arriving home on Ethiopian government charter flights from the Kingdom of Saudi Arabia (KSA) over the past 12 days.

According to IOM, it provides the returnees, who are returning with up to 12 charters a day from the KSA to Addis Ababa, with overnight accommodation, food, water, shoes and money for transport to their places of origin. It added and said that the exact number of Ethiopian migrant workers in the KSA was unknown, but the Ethiopian government expects more to return in the coming months.

IOM indicated that it will need approximately USD 4.5 million to adequately support 30,000 returnees. This figure could increase in coming weeks depending on the actual number of arrivals.

Arab News on its part reported that the Saudi government was covering the costs of returning migrants and there is a plan to repatriate 32,000 Ethiopians within the coming days. More 50,000 Ethiopians will be returned in the coming days.

What the Ethiopian government has been doing for the returning migrants has not been known so far. “if IOM and the Saudi government are covering the costs?” Some observers ask, “then is the sole role of the Ethiopian government to stand for photographs with the returnees?”.

An employee of the Ethiopian Airlines said that the migrants are being brought back by IOM whereas the Ethiopian Minister of Foreign Affairs and other ministers are busy having photographs with the returnees.
 posted by samuale Tewelde

Attacks on Ethiopians in Saudi worsen







http://ethsat.com/2013/11/29/attacks-on-ethiopians-in-saudi-worsen/

ESAT News  November 29, 2013

Many Ethiopians in Saudi Arabia, who spoke to ESAT, have said that several thousands of Ethiopian migrants are still languishing in concentration camps known as Setreh, in Saudi Arabia.

Thirsty and hungry pregnant women, children and mothers are calling for help. Those that leave the camps to buy foods and drinks are being killed, said friends of those killed.

ESAT’s reporter in Addis Abeba said IOM has been covering the medical treatment costs of the returnees and most suffer from psychological and physical traumas.

Meanwhile, protests opposing the treatment of Ethiopian migrant workers in Saudi Arabia have continued. Ethiopians residing in Sweden had protested outside the Ethiopian Embassy on Wednesday and brunt the photographs of the Saudi King Abdullah.

On Thursday, Ethiopians residing in Spain had protested outside the Saudi Embassy in Madrid. The protesters have also submitted their complaint to the representative of the Embassy.
         posted by samuale Tewelde

 

«እንጀራ ከአልጫ እና ከቀይ ወጥ ጋር ወይንም ሞት»








ከዳንኤል ክብረት
«እንጀራ ከአልጫ እና ከቀይ ወጥ ጋር ወይንም ሞት»
የዛሬ ሁለት ዓመት በ2000 ዓም ነው፡፡ የገና በዓል አልፎ በቀጣዩ እሑድ፡፡ ከዚህ በፊት አጋጥሞኝ የማያውቅ አንድ አዲስ መርሐ ግብር ላይ ለመሳተፍ ጓጉቻለሁ፡፡ ባለፉት ሃያ ዓመታት በተለያዩ መድረኮች ላይ የዐቅሜን ያህል «አስተምሬያለሁ»፡፡ የዚህኛው ግን ይለያል፡፡
በጠዋቱ ዲያቆን ምንዳየ ብርሃኑ ቤቴ ድረስ መጥቶ በመኪናው ይዞኝ ሄደ፡፡ ስለ መርሐ ግብሩ እየተነጋገርን እና ይህንን ዕድል በማግኘታችን ዕድለኞች መሆናችች እያነሣን በቀለበት መንገድ ከነፍን፡፡ መርሐ ግብሩን ለፈቀዱት የማረሚያ ቤት ባለ ሥልጣናትም ምስጋናችንን አቀረብን፡፡ በማረሚያ ቤቶች ውስጥ እንዲህ ያለ የማናስበው ነገር በመደረጉ እዚህች ሀገር ውስጥ ሳናውቃቸው የተቀየሩ ነገሮች አሉ ማለት ነው) እያልን ነበር የምንጓዘው፡፡
እነሆ ቃሊቲ የሚገኘው ዋናው ማረሚያ ቤት በር ላይ ደረስን፡፡ እንደኛ ለመርሐ ግብሩ የተዘጋጁ እናቶች፣ እኅቶች፣ ወንድሞች አየን፡፡ ራቅ ብለው ደግሞ በወቅቱ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቡነ ይስሐቅ ከአንድ አባት ጋር መኪና ውስጥ ተቀምጠዋል፡፡
ለመግባት የሚያስፈልገን ሂደት ተጠናቀቀና በብጹእ አባታችን መሪነት ወደ ውስጥ ገባን፡፡ እኔ በዚህ መልኩ ወደ ማረሚያ ቤት ስገባ የመጀመርያዬ ነበር፡፡ እያንዳንዷን ነገር በንሥር ዓይን ነበር የማያት፡፡ እየሄድኩ ያለሁት በታሪክ መንገድ ላይ ነበርና፡፡
አንድ ትልቅ በር ተከፈተልንና በፖሊሶቹ አስተናጋጅነት ወደ ውስጥ ዘለቀን፡፡ የፖሊሶቹ መስተንግዶ ለመስተንግዶ ተብለው በተቀጠሩት አስተናጋጆች ዘንድ እንኳን የማይገኝ ዓይነት ነበር፡፡
ገባን፡፡
ዙርያውን በተገጠገጠ ቤት የተከበበ ግቢ ነው፡፡ ቤቱ በአራት መዓዝን ሪጋ የተሠራ ነው፡፡ ከቤቱ ፊት ለፊት መሐል ሜዳውን ከብቦ የግቢ አትክልት አስውቦታል፡፡ መካከለኛው ሜዳ ጽድት ብሎ ማረሚያ ቤት መሆኑን ያስረሳል፡፡ በሜዳው መካከል በቆርቆሮ ተሠርቶ በመስተዋት የተዋበ፣ በመጋረጃም የተጋረደ ሥዕል ቤት አለ፡፡
እኛ ስንገባ አንድ አረጋዊ ሰው ሄደው መጋረጃውን ገለጡት፡፡ አቡነ ይስሐቅ እንደ ቆሙ ጸሎት አደረሱ፡፡ ሁሉም በተጠንቀቅ ቆመዋል፡፡ ጸሎቱ እንዳበቃ በተዘጋጀልን መቀመጫ ተቀመጥን፡፡ ምንዳዬ ከአቡነ ይስሐቅ ጎን፣ እኔም ከምንዳዬ ጎን ተቀመጥን፡፡
በዚህ ጊዜ ጋቢ የለበሱ እና መቋሚያ የያዙ አንድ አዛውንት ከጎኔ መጥተው ቁጭ አሉ፡፡ ልቤ አንዳች ነገር ያወቀ መሰለው፡፡ መርሐ ግብሩን ያስተናግድ የነበረውን ልጅ ጠራሁትና በኋላዬ በኩል ጠየቅኩት፡፡ በአዎንታ ራሱን ነቀነቀ፡፡
ክው አልኩ፡፡
ከጎኔ የተቀመጡትን ሰው ለመጀመርያ ጊዜ በአካል ማየቴ ነው፡፡ የሦስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ባደግኩበት አካባቢ መጥተው ነበር፡፡ ያኔ ሲመጡ የሙዚቃ አስተማሪያችን የሰልፍ መዝሙር አስጠንተውን በከተማዋ መግቢያ መንገድ ላይ ተሰልፈን ነበር የተቀበ ልናቸው፡፡ እጅግ ብዙ መኪኖች ተከታትለው አልፈው መዝሙራችንን አበቃን፡፡ የተቀበልናቸው ሰው ማንኛው እንደሆኑ ለማየት አልቻልንም ነበር፡፡ ብቻ ስማቸውን በተከ ታታይ ሰምተናል «ጓድ ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስ» እየተባለ ሲነገር፡፡
እነሆ አሁን ከጎኔ የተቀመጡት እርሳቸው ናቸው፡፡ በቴሌቭዥን አይቻቸው ዐውቃለሁ፡፡ የዛሬው ግን የተለየ ነበር፡፡ ወተት የመሰለ ነጭ ጋቢ ለብሰው፤ ወዝ የጠገበ መቋሚያ ይዘዋል፡፡ ትንሽ እንደማመም ያደረጋቸው ይመስላል፡፡ በግራ እጃቸው የተደጎሰ ዳዊት አለ፡፡
ምንዳዬ መዝሙር ሲዘምር ፍቅረ ሥላሴም አብረው ይዘምሩ ነበር፡፡ ምን እርሳቸው ብቻ፣ ለገሠ አስፋው፣ ፍሥሐ ደስታ፣ ሌሎቹም ሁሉ እያሸበሸቡ እና እያጨበጨቡ አብረውት ነበር የሚዘምሩት፡፡ እነዚህ ትናንት ሀገሪቱን ሲመሩ የነበሩ፤ በተለየ ታሪካቸው የምናውቃቸው፤ ቀይ ሽብር እና ነጭ ሽብር በዘመናቸው የተፈጸመ፡፡ በብዙ የሀገሪቱ መከራዎች ወስጥ ተጠያቂዎች የሆኑ ሰዎች ዛሬ ስታዩዋቸው እንደዚያ አይደሉም፡፡
የበዓሉ መዓድ ከመቆረሱ በፊት ጸሎት ተደርጎ ነበር፡፡ መጀመርያ ውዳሴ ማርያም ተደገመ፡፡ እኛ አይደለንም የደገምነው፡፡ መቋሚያቸውን ተደግፈው እነዚህ ታላላቅ የደርግ ባለ ሥልጣናት ናቸው የደገሙት፡፡ በአማርኛ እንዳይመስላችሁ፤ በግእዝ፡፡ የኪዳኑን ጸሎት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው የሚቀበሉት እነርሱ ነበሩ፡፡
ትምህርት ሲሰጥ ሁሉም ጎንበስ ብለው ያነቡ ነበር፡፡ እኔ ከአሥራ አምስት ደቂቃ በላይ ማስተማር አልቻልኩም፡፡ የእነዚያን ሰዎች ዕንባ አይቼ መቆም አቃተኝ፡፡ ምናልባት እኛ ይቅር አላልናቸው ይሆናል፡፡ እግዚአብሔር ግን መሐሪ ነውና ይቅር እንዳላቸው ርግጠኛ ነበርኩ፡፡ በየቀኑ ኪዳን ይደረሳል፡፡ ዳዊት ይደገማል፡፡ ካህን አላቸው፡፡ ንስሐ ገብተዋል፡፡ ብዙዎቹ ቆራቢዎች ናቸው፡፡ ላለፉት ሃያ ዓመታት በዚህ መልኩ እግዚአብሔርን ተማጽነዋል፡፡ ታድያ እግዚአብሔር ዝም ይላል እንዴ፡፡
ምን ብዬ ላስተምራቸው? ኑሮ ራሱ አስተምሯቸዋል፡፡ ሕይወት ራሱ ለውጧቸዋል፡፡ ድምፁን ከውጭ ሳይሆን ከውስጥ ሰምተውታል፡፡ መስማትም ብቻ ሳይሆን አይተውታል፡፡ በየቀኑ ከእርሱ ጋር ይነጋገራሉ፤ እና ምን ልበላቸው? ኑሮውም፣ ጤናውም፣ ሃሳቡም አስረጅቷቸዋል፡፡
እነሆ ይህ ሥዕል በአእምሮዬ ተቀርጾ ይኖር ስለነበር በየጊዜው እነዚህ ሰዎች ይቅርታ ሊደረግላቸው ይገባል እያልኩ እንድናገር አድርገውኛል፡፡ አሁን ደግሞ መልካም ዜናዎችን እየሰማን ነው፡፡
ይህንን ነገር ላደረጉ የእምነት ተቋማት፤ በጎ ፍቃደኛነቱን ላሳየው መንግሥት፣ ተባባሪ ሆነው ታሪክ እየሠሩ ላሉ ተጎጅዎች የምናመሰግንበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡
እዚህ አሜሪካ ከመጣሁ ጀምሮ በየሬዲዮው፣ ፓልቶኩ፣ ዌብ ሳይቱ፣ ክርክሩ በዚህ ጉዳይ ላይ ሆኗል፡፡ ከሀገር ቤት እየደወሉ የሚከራከሩም ሰዎች አሉ፡፡
አንዳንድ ጊዜ «የምንፈልገውን ሁሉ ካላገኘን ምንም ነገር ባናገኝ ይሻላል» የሚል ዓይነት ክርክር እሰማለሁ፡፡ ዕርቁ እገሌን እና እገሌን የማያካትት ከሆነ፤ እነ እገሌም ካልተጨመሩበት ባይፈቱ ይሻላል ይባላል፡፡ ጎበዝ በዚህ ሁኔታ ስንናገር እግራችንን በተጎጅዎች መሬት ላይ እና በእሥረኞቹ መሬት ላይ ማቆም አለብን፡፡
«ወይ መሬት ላይ ያለ ሰው» አለ፡፡
የእነርሱ በዚሀ ሁኔታ ካለቀ የነ እገሌም ይጨመርበት ይባላል እንጂ «እንጀራ ስትሰጡኝ ከቀይ ወጡ ጋር አልጫ ከሌለው ረሃብ ይሻላል» ይባላል እንዴ፡፡ መጀመርያ ለእንጀራው እና ለቀይ ወጡ እናመስግን፤ ከዚያ ደግሞ አልጫ እንዲጨመር እንጠይቅ፡፡ «እንጀራ ከአልጫ እና ከቀይ ወጥ ጋር ወይንም ሞት» የሚለው መፈክር አሁንም አልለቀቀንም እንዴ፡፡
የይቅርታውን ሂደት የሚያከናውኑትን የሃይማኖት ተቋማትም ማመስገን፤ በርቱ ሥራችሁ የሚያስመሰግን ነው ብሎ ማበረታታት ይገባል፡፡ ባጠፉበት የምንወቅሳቸውን ያህል ሲያለሙ ማመስገን አለብንኮ፡፡ እናንተ ማን ናችሁና ይህንን ታደርጋላችሁ? እያሉ መራቀቅ ከአእምሮ ጅምናስቲክ ያለፈ ዋጋ የለውም፡፡ ማሩ ንጹሕ ነወይ? ከማለት ይልቅ ማሩን ማን አመጣው? እያሉ መወዛገብ በኅሊና ላይ ሌላ እሥር ቤት መክፈት ነው፡፡
በጎን ነገር ማንም ይሥራው፤ ከቻለ ሰይጣንም ይሥራው፤ ከሠራው ይደነቃል፣ ይመሰገናል፤ እነዚህ ተቋማት የሚችሉትን ሁሉ አድርገው እውነት እንደተባለው የይቅርታው ሂደት ከተከናወነ እሥረኞቹ ብቻ ሳይሆኑ እነርሱም ናቸው ከስንፍና የሚፈቱት እና ልናግዛቸውም፣ ልናደንቃቸውም ግድ ይለናል፡፡
መንግሥትም ቢሆን ሊመሰገን ይገባዋል፡፡ ይህንን ታሪክ በይቅርታ እና በዕርቅ ለመዝጋት በጎ ፈቃድ ካሳየ እሰዬው ነው፡፡ አጠፋ ሲባል ባገኘነው መንገድ ሁሉ ለመውቀስ የምንተጋ ሰዎች ሲያለማ ደግሞ ለማመስገን መሽቀዳደም አለብን፡፡
ግማሽ ብርጭቆ ውኃ የያዘውን ብርጭቆ ከየት በኩል ነው ማየት ያለብን? ለመሆኑ ብርጭቆው ግማሽ ሙሉ ነው ወይስ ግማሽ ጎደሎ?
አንዳንድ ጊዜ ዕንቁላሉን ተከባክቦ፣ ሙቀት ሰጥቶ እና ከድመት ጠብቆ ዶሮ እንዲሆን ከመርዳት ይልቅ «እኔ ዶሮ ነበር የምፈልገው» እያሉ ዕንቁላሉን የመስበር አባዜ ያለብን ይመስላል፡፡ የተገኘውን በጎ ነገር ይዞ፣ እርሱን አጎልብቶ፣ የቀረውን ችግር ለመፍታት ከመጓዝ ይልቅ ያለውንም አጠፋፍቶ በዜሮ መጫወት ምን ይሉታል?
የተጎጅ ቤተሰቦች ይህንን ታሪካዊ ሥራ ለመሥራት ስትነሱ ሕመማችሁን እናውቃለን፤ ጉዳታችሁም ይሰማናል፡፡ ከእኛ ይልቅ ለእናንተ ሁኔታው ከባድ ነው፡፡ ግን እየሠራችሁ ያላችሁት የጀግንነት ሥራ ነውና እናደንቃችኋለን፡፡ በእምነት ጽድቅ፣ በታሪክ ክቡር፣ በባህል ምስጉን የሆነ ሥራ ነውና በርቱ፡፡
የዕርቁን ሂደት የምታከናውኑ የእምነት ተቋማትም ይህንን ነበርና ስንጠብቅባችሁ የኖር ነው ይበልጥ አጠናክራችሁ ቀጥሉ፡፡ መጀመርያ የጀመራችሁትን ለፍጻሜ አድርሱ፡፡ ከዚያ ደግሞ የሚቀራችሁን ትሠራላችሁ፡፡ ከምትሰሙት ይልቅ የምትሠሩት ውጤት ያመጣልና ወደ ኋላ አትበሉ፡፡
መንግሥትም ይህንን ታሪክ ሀገርን በሚያኮራ፤ ወገንን በሚያረካ እና ስማችንን በዓለም ላይ ከፍ በሚያደርግ መልኩ ለመዝጋት ያሳየኸውን በጎ ፈቃድ ለውጤት አብቃው፡፡ ሌሎች መሠራት ያለባቸው፤ መሆን የነበረባቸው ነገሮች ይኖሩ ይሆናል፡፡ አሁን ግን እየሆነ ካለው ነገር እንነሣ፡፡ ምናልባት ይህ ታሪክ በራሱ ታሪክ ከመሆኑም በላይ ለሌላውም ታሪካችን በር የሚከፍት ታሪክ ሊሆን ይችላልና፡፡
የተጀመረው ይሳካ፣ ያልተጀመረውም ይቀጥል፡፡
ሁላችሁም እባካችሁ ክርክሩ ሰኞ ዕለት አልቆ ውዳሴውን ለመስማት አብቁን፡፡

በሳውዲ ለሚገኙ ወገኖቻችን በአፋጣኝ እንድረስ፤ በወያኔ ላይ በጋራ እንነሳ!!!

/

http://www.ginbot7.org/2013/11/22/

በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው መጠን የለሽ የመብት ጥሰት ለመቃወም በተለያዩ የዓለም አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በየአገራቱ የሚገኙ የሳውዲን ኢምባሲዎችን በተቃውሞ እያጨናነቁ ነው። በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ባለው ዘግኛኝ በደል የተሰማቸውን ጥልቅ የመጠቃት ስሜት ኢትዮጵያን በተቃውሞ ሰልፎቹ ላይ በሚያሰሟቸው መሪር የሐዘን እንጉሮችና የቁጭት ንግግሮች እየገለፁ ነው። ከሐዘንና ቁጭት ባለፈም ለበደል ለተጋለጡ ወገኖቻችን አስቸኳይ ሰብዓዊ ርዳታ ለማድረስ እና የዲፕሎማሲ ድጋፍን ለማሰባሰብ ዓለም ዓቀፍ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ሥራውን ጀምሯል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህንን ዓለም ዓቀፍ ጥረት ለመደገፍ በውጭ አገራት የሚገኙ አባላቱ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መመሪያ አስተላልፏል።
ይህ ሁሉ በውጭ አገራት እየተደረገ ያለ ጥረት ነው። ኢትዮጵያዊያን ባሉበት አገራትና ከተማዎች ሁሉ በዚህ ጉዳይ ላይ በአንድነት መንቀሳቀሳቸው የሚያስደስት ነገር ነው። ሌላው ቀርቶ በሳዉዲ ዋና ከተማ ሪያድ ውስጥ እንኳን ኢትዮጵያውያን የሳውዲን መንግሥት ተቃውመው ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል።
የሳውዲ መንግሥት በኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ የያዘውን ጨካኝ አቋም እና በመንግሥት እውቅና በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል መቃወም ያልተቻለው በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ!!! ይህ እጅግ ያማል፣ ልብን ያደማል።
ወያኔ የሳውዲ የንግድ ሸሪኮቹን ለማስደሰት የፈንሳይን ግማሽ የሚያህል ለም መሬት በነፃ መስጠቱ በቂ አልመሰለውም። በአገራቸው ኢትዮጵያዊያንን ሲጨፈጭፉ፣ ሲገሉና ሲደፍሩ በቸልታ መመልከቱ በቂ የወዳጅነት ስጦታ መስሎ አልተሰማውም። እናም ሸሪኮቹ የበለጠ እንዲደሰቱና ከእስከዛሬ በበለጠ ገንዘብ እንዲደጉሙት ለማበረታታት አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲያቸው ፊት ለፊት ኢትዮጵያንን ደበደበላቸው።
ወያኔ ከሳውዲ ጋር ያለው ግኑኝነት “የቢዝነስ ሽርክና” ነው። ቢዝነሱም ኢትዮጵያዊያንን በቁማቸው መሸጥንም ያጠቃልላል። የወያኔ ሹማምንት እና የሳውዲም ቱጃሮች በዘመናዊ ባርነት ንግድ ውስጥ አቀባይና ተቀባይ ናቸው። ለዚህም ነው እየተነገደበት ያለው ምስኪን ኢትዮጵያዊ እጣ ፈንታ በአዲስ አበባና በሪያድ አንድ ዓይነት የሆነው። እዛ ዱላ፤ እዚህም ዱላ። እዛ እስር፤ እዚህም እስር። እዚያ ስድብ፤ እዚህም ስድብ። እዚያ ቶርቸር፤ እዚህም ቶርቸር። በባርያ ንግድ ውስጥ አቀባዩም ተቀባዩም ባርያዉን መግዛታቸው፣ መስበራቸው፣ መግደላቸው የማይቀር መሆኑ የታወቀ ነው።
ሌላው አሳዛኝ ጉዳይ ደግሞ የወያኔ ድኩማን ሹማምንት የሚሰጡት አስተያየት መስማት ነው። በሳውዲ ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ፍትህ ለመጠየቅ በመላው ዓለም እና በአዲስ አበባ ደግሞ በሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪነት ወደ ጎዳና በወጡ ኢትዮጵያዊያን የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ተብየው “የፋሺሽት መፈክር አንግቦ በተጎሳቆሉ ዜጎች ስም የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት መጣር ብሎም መንግሥት በዜጎቹ ግዴለሽ እንደሆነ አስመስሎ ማቅረብ” ሲል ተሳልቋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተብየው ጨምሮ ሁሉም የወያኔ ሹማምንት “ሳውዲዎች በግዛታቸው ውስጥ ያሻቸውን የማድረግ “ሉዓላዊ” መብት አላቸው፤ መንግሥታችን የሳውዲ አረቢያን ሉዓላዊ መብት ያከብራል” እያሉ ይከራከራሉ። ለመሆኑ ይህንን የሚሉት ከልባቸው ነው? ፈጽሞ። ኢትዮጵያዊያንን ማሰቃየትና መግደል የቢዝነሳቸው አካል ስለሆነ ነው እንጂ የሉዓላዊነት ትርጉም ይህን ያህል ተምታቶባቸው አይደለም።
ሰብዓዊ መብቶች አገር፣ ድንበር፣ ዜግነት፣ ወይም ሌላ ማናቸው ሰው ሠራሽ ህግጋት ሊጥሷቸው እንደማይገቡ የወያኔ ሹማምንት ቢያንስ ሲነገር ሰምተው ያውቃሉ። ማንኛውም ሰው ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ መገደል፤ ሰቆቃ (ቶርቸር) እንዲደርስበት ማድረግ፤ ጾታዊ ጥቃት እንዲደርስበት ማድረግ እንደማይቻል ሰምተው ያውቃሉ። ሰብዓዊ መብቶች ሰዎች ሰው በመሆናቸው ብቻ ሊያገኙት የሚገባ ክብር መሆኑ በተሳተፉባቸው በርካታ ዎርክ ሾፖች ሰምተዋል። ያም ሆኖ ግን በዘመናዊው ዓለም እንስሳ እንኳን ያገኘውን ክብር ኢትዮጵያዊያን ተነፍገው በሪያድ ጎዳናዎች ሲታረዱ፤ በጭካኔ ሲደበደቡና ሲገረፉ፤ ሴቶች ሲደፈሩ፤ ሕፃናት በረሀብና በእርዛት ሲቀጡ የወያኔ ባለሥልጣኖች የበዳዮች አፈቀላጤ ሆነው የሚከራከሩት በዳዮቹ ሸሪኮቻቸው ስለሆኑ ነው።
ይህ ድርጊት በወያኔ እየደረሰብን ያለው በደል ምን ያህል ሥር የሰደደ እንደሆነ እና የኢትዮጵያዊያን ሰቆቃ ምንጭ የት እንዳለ አመላካች ሆኗል።
“ትግላችን የነፃነት ትግል ነው” ስንል “ከማን ነፃ ለመውጣት?” እያሉ የሚሳለቁ እንደነበሩና እንዳሉም ይታወቃል። በወያኔ አገዛዝ ኢትዮጵያዊያን ወደ ባርነት ማሽቆልቆላቸው ይህ ተጨባጭ ማስረጃ ነው። ከወያኔ የባርነት አገዛዝ ነፃ እስካልወጣን ድረስ ሌሎች አገሮች መብቶቻችን የሚያከብሩልን በየአገራቱ ልምድ እና ከወያኔ ጋር ባላቸው ሽርክና መጠን ነው።
ለሳውዲ መንግሥትና ቱጃሮቹ ከነዳጅ ቀጥሎ የሀብታቸው ምንጭ ከየአገሩ የሚመጣላቸው የድሀ ጉልበት ነው። የሳውዲ ቱጃሮች ድሆችን ከባርነት ባልተሻለ መንገድ ረግጠው በመግዛት ኑሮዓቸውን ያደለቡ ናቸው። ለወያኔ አገዛዝ ደግሞ ከቡና ቀጥሎ ከፍተኛው የገቢ ምንጩ ዜጎቹን በመሸጥ የሚሰበስበው ነው። ለወያኔ፣ ኢትዮጵያዊያን ወንዶችና ሴቶች ትርፍ አምጪ ሸቀጦች ናቸው። ወያኔና ሳውዲ – ሻጭና ገዢ ናቸው።
ባርያ ከሻጩ ነፃ ሳይወጣ ከአንድ ገዢ ነፃ ቢወጣ ሌላ ገዢ ስለሚመጣ ዘለቄታነት የለውም። እኛም ከወያኔ ነፃ ሳንወጣ ከሳውዲ ነፃ መወጣት አይቻለንም፤ ቢቻልም ነፃነታችን ዘላቂነት አይኖረውም።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በሳዉዲ አረቢያ በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ በሚደርሰው ጥቃት ክፉኛ ተቆጥቷል። በዚህ የመከራና ጭንቅ ሰዓት ለወገኖቻችን ለመድረስ የሚቻለውን ጥረት ሁሉ ማድረግ እንዳለብን ያምናል። አባላቱ በነብስ አድን ርብርብ በግንባር ቀደምትነት እንዲሳተፉ መመሪያ አስተላልፏል። ይህ አጣዳፊ ሆኖም ጊዜዓዊ መፍትሔ ነው። በግንቦት 7 እምነት የችግሮቻችን ሰንኮፍ ያለው አዲስ አበባ ነው። ሰንኮፉን ሳንነቅል የሚደርስብንን ውርደት በዘላቂነት መቀልበስ አንችልም። ስለሆነም በችግር ላይ የወደቁትን ወገኖቻችን እየረዳን፤ የችግሮቻችን ምንጭ በሆነው ወያኔ ላይ የተባበረ ክንዳችንን እናንሳ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ  ህዝብ!
   posted by samuale Tewelde